ደቡብ ሱዳን ከዓለም አቀፍ ግፊት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አጠቃላይ ምርጫ ልታካሂድ ቀጠሮ ቆረጠች | ከይር ታይምስ
አምዶች
የቅርብ ዜና
ደቡብ ሱዳን ከዓለም አቀፍ ግፊት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አጠቃላይ ምርጫ ልታካሂድ ቀጠሮ ቆረጠች ግዙፉ የፈረንሳይ የነዳጅ ኩባንያ ቶታል ኢነርጂ ከ75 ዓመታት ቆይታ በኋላ ከኢትዮጵያ ሊወጣ ነው ባይናንስ በኢትዮጵያ ውስጥ አቋርጦት የነበረውን የክሪፕቶ ከረንሲ ግብይት አገልግሎት በድጋሚ ጀመረ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በክርስቲያን ታደለ እና ዮሐንስ ቧያለው መዝገብ ላይ ሊሰጥ የነበረውን ብይን አዛወረ በኬንያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ የወሮበላነት ፖለቲካ (Goonism) በመባል የሚታወቀው ተግባር፣ በተደራጀ መልክ ተዋቅሮ ዳግም ማንሰራራቱ ተገለጠ። የመካከለኛው ምስራቅ ባሩድ ተቀሰቀሰ፡ ኢራን መርከቦች ወደ ሆርሙዝ እንዳይጠጉ አስጠነቀቀች ህወሃት በአሜሪካ የቪዛ ገደብ ላይ ያለውን ቅሬታ ገለጸ፤ የፕሪቶሪያው ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲተገበርም ጠየቀ በትምህርት ላይ ያረበበው የጦርነት ጥላ፡ በኢትዮጵያ የነገይቱ ተስፋዎች መፃኢ ዕድል ሲፈተን የመንግስት ካዝና እስከመቼ ይዘረከረካል? 15 ቢሊዮን ብር ያላግባብ የያዙት ተቋማት በሕግ ፊት ይቁሙ! አዲሱ የሕወሓት እና የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ግጭት 600 ሺህ ሰዎችን የበላውን ጦርነት ሊቀሰቅስ እንደሚችል ስጋት ፈጠረ ደቡብ ሱዳን ከዓለም አቀፍ ግፊት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አጠቃላይ ምርጫ ልታካሂድ ቀጠሮ ቆረጠች ግዙፉ የፈረንሳይ የነዳጅ ኩባንያ ቶታል ኢነርጂ ከ75 ዓመታት ቆይታ በኋላ ከኢትዮጵያ ሊወጣ ነው ባይናንስ በኢትዮጵያ ውስጥ አቋርጦት የነበረውን የክሪፕቶ ከረንሲ ግብይት አገልግሎት በድጋሚ ጀመረ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በክርስቲያን ታደለ እና ዮሐንስ ቧያለው መዝገብ ላይ ሊሰጥ የነበረውን ብይን አዛወረ በኬንያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ የወሮበላነት ፖለቲካ (Goonism) በመባል የሚታወቀው ተግባር፣ በተደራጀ መልክ ተዋቅሮ ዳግም ማንሰራራቱ ተገለጠ። የመካከለኛው ምስራቅ ባሩድ ተቀሰቀሰ፡ ኢራን መርከቦች ወደ ሆርሙዝ እንዳይጠጉ አስጠነቀቀች ህወሃት በአሜሪካ የቪዛ ገደብ ላይ ያለውን ቅሬታ ገለጸ፤ የፕሪቶሪያው ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲተገበርም ጠየቀ በትምህርት ላይ ያረበበው የጦርነት ጥላ፡ በኢትዮጵያ የነገይቱ ተስፋዎች መፃኢ ዕድል ሲፈተን የመንግስት ካዝና እስከመቼ ይዘረከረካል? 15 ቢሊዮን ብር ያላግባብ የያዙት ተቋማት በሕግ ፊት ይቁሙ! አዲሱ የሕወሓት እና የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ግጭት 600 ሺህ ሰዎችን የበላውን ጦርነት ሊቀሰቅስ እንደሚችል ስጋት ፈጠረ
ዜና / ዓለም አቀፍ ዜና

ደቡብ ሱዳን ከዓለም አቀፍ ግፊት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አጠቃላይ ምርጫ ልታካሂድ ቀጠሮ ቆረጠች

June 23, 2026

ደቡብ ሱዳን ከከባድ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ጫና እና ግፊት በኋላ፣ አገሪቱ ነጻነቷን ካገኘች ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን አጠቃላይ ምርጫ በሚቀጥለው ዓመት ታኅሣሥ ወር ላይ ለማካሄድ ቀን መቁረጧን አስታወቀች።

​ነገር ግን ቀድሞ የአገሪቱ የመጀመሪያ ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩትና በአሁኑ ወቅት በትግል ላይ በሚገኙት ዶ/ር ሬክ ማቻር የሚመራው ትልቁ ተቃዋሚ ቡድን ይህንን ውሳኔ ተቃውሟል። ተቃዋሚው ወገን በፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር መንግሥት እና በእነሱ መካከል ያሉ መሠረታዊ የፖለቲካና የጸጥታ ችግሮች ሳይፈቱ የምርጫ ቀን መቁረጥ አደገኛ አካሄድ ነው ሲል ስጋቱን ገልጿል።

​በአሁኑ ወቅት "የአገር ክህደት" ክስ ተመስርቶባቸው አሁንም ድረስ በእስር ላይ የሚገኙት ሬክ ማቻር፣ በምርጫው ላይ በነጻነት ለመወዳደር ከእስር እንደሚፈቱ ወይም እንደማይፈቱ መንግስት እስካሁን በግልጽ ያለው ነገር የለም።

​አሜሪካን ጨምሮ በርካታ የምዕራባውያን አጋሮች፣ ዋናው የተቃዋሚ መሪ ሬክ ማቻር በእስር ላይ እያሉ በአገሪቱ ውስጥ የሚደረግ ማንኛውም ፖለቲካዊ ሂደትና ምርጫ ተቀባይነት የለውም የሚል አቋማቸውን በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል። ደቡብ ሱዳን ነጻነቷን ካገኘች ማግስት ጀምሮ በገጠማት የእርስ በርስ ጦርነትና አለመረጋጋት ምክንያት እስካሁን አጠቃላይ ምርጫ አድርጋ አታውቅም።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ