«ልመና በቃን፤ ወደ ቀድሞ ቀያችን ተመልሰን ራሳችንን መርዳት እንፈልጋለን» - ተፈናቃዮች |
አምዶች

የዲጂታል ዜናዎች ዕምብርት

የቅርብ ዜና
የመንግስት ካዝና እስከመቼ ይዘረከረካል? 15 ቢሊዮን ብር ያላግባብ የያዙት ተቋማት በሕግ ፊት ይቁሙ! አዲሱ የሕወሓት እና የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ግጭት 600 ሺህ ሰዎችን የበላውን ጦርነት ሊቀሰቅስ እንደሚችል ስጋት ፈጠረ ሕገ-ወጥ የኪራይ ጭማሪ እና ስንብት ፍርድ ቤት ያቆማል ተባለ የምርጫ ቦርድ የ723 ምርጫ ክልሎችን ውጤት አፀደቀ፤ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይፋዊ ማጠቃለያ ሰኔ 14 ቀን ይገለጻል በአማራ ክልል በደረሰ አስከፊ የመኪና አደጋ የ31 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በ33 ላይ ጉዳት ደረሰ ታዋቂው የባህላዊ ሙዚቃ አቀንቃኝ አርቲስት ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ በአዲስ አበባ የተጀመረው አስገራሚ የቤት ግንባታ አብዮት! | አዲሱ የዳያስፖራ የቤት ቁጠባ መረጃ (10/70) የብልፅግና ፓርቲ በቁልፍ ክልሎች አሸነፈ፤ ከፊል የምርጫ ውጤቶች ይፋ ሆነዋል የቀይ ባህሩ ቼዝ፣ "የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው" በትሪሊዮኖች የተሰናዳው የ2019 ረቂቅ በጀት ማንን ይታደጋል? የመንግስት ካዝና እስከመቼ ይዘረከረካል? 15 ቢሊዮን ብር ያላግባብ የያዙት ተቋማት በሕግ ፊት ይቁሙ! አዲሱ የሕወሓት እና የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ግጭት 600 ሺህ ሰዎችን የበላውን ጦርነት ሊቀሰቅስ እንደሚችል ስጋት ፈጠረ ሕገ-ወጥ የኪራይ ጭማሪ እና ስንብት ፍርድ ቤት ያቆማል ተባለ የምርጫ ቦርድ የ723 ምርጫ ክልሎችን ውጤት አፀደቀ፤ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ይፋዊ ማጠቃለያ ሰኔ 14 ቀን ይገለጻል በአማራ ክልል በደረሰ አስከፊ የመኪና አደጋ የ31 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በ33 ላይ ጉዳት ደረሰ ታዋቂው የባህላዊ ሙዚቃ አቀንቃኝ አርቲስት ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ በአዲስ አበባ የተጀመረው አስገራሚ የቤት ግንባታ አብዮት! | አዲሱ የዳያስፖራ የቤት ቁጠባ መረጃ (10/70) የብልፅግና ፓርቲ በቁልፍ ክልሎች አሸነፈ፤ ከፊል የምርጫ ውጤቶች ይፋ ሆነዋል የቀይ ባህሩ ቼዝ፣ "የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው" በትሪሊዮኖች የተሰናዳው የ2019 ረቂቅ በጀት ማንን ይታደጋል?
ዜና / የሀገር ውስጥ ዜና

«ልመና በቃን፤ ወደ ቀድሞ ቀያችን ተመልሰን ራሳችንን መርዳት እንፈልጋለን» - ተፈናቃዮች

በኢሳያስ ገላው | June 18, 2026

ከኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ጃርቴ ዞን ተፈናቅለው በአማራ ክልል በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች የሰፈሩ ወገኖች፣ ላለፉት ስድስት ዓመታት በከፋ ሁኔታ ውስጥ መቆየታቸውን ገልጸው፤ ወደ ቀድሞ ቀያቸው ተመልሰው ራሳቸውን እንዲረዱ ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጥሪ አቀረቡ።

በደቡብ ወሎ ዞን በጃራ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች ለጋዜጣው እንደገለጹት፤ ለዓመታት በእርዳታ እጅ መጠበቅ ለስነ-ልቦናዊና ማህበራዊ ቀውስ ዳርጓቸዋል። «ጥያቄያችን ግልጽ ነው፤ ወደ ተወለድንበትና ወደ አደግንበት ቦታ መልሱን፤ ሰርተን ራሳችንን እንደግፍ፤ ልመና በቃን» ሲሉ የችግሩን አሳሳቢነት አስረድተዋል። ተፈናቃዮቹ አክለውም፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት የጸጥታና የመሠረተ ልማት ሁኔታዎችን በማመቻቸት ወደ ቀድሞ ይዞታቸው እንዲመልሷቸው በፅኑ ጠይቀዋል።

የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ሥራ አመራር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወይዘሮ ሰርካዲስ አታሌ በበኩላቸው፣ በመጠለያ ጣቢያና ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ ወገኖችን የመመለስ ጉዳይ በትኩረት እየተሠራበት መሆኑን ገልጸዋል። «ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ ከኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አከናውነናል» ብለዋል።

ሆኖም ምክትል ኮሚሽነሯ አያይዘው እንደገለጹት፤ መንግሥት ሁሉንም ተፈናቃዮች የመመለስ ፍላጎት ቢኖረውም፣ የተመላሾችን ደህንነት አስተማማኝ በሆነ መልኩ ማረጋገጥ ቀዳሚውና ወሳኙ ተግባር መሆኑን አመልክተዋል። የጸጥታ ሁኔታው ተፈትሾና ተመላሾች በሰላም መኖር የሚችሉበት ሁኔታ ሲረጋገጥ የመመለስ ሂደቱ እንደሚፋጠን ጠቁመዋል።

በአሁኑ ወቅት ከኦሮሚያና ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በደቡብ ወሎና በሰሜን ወሎ ዞኖች የሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥር ከ64 ሺህ በላይ መሆኑን የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ተፈናቃዮቹ አሁንም በቂ ሰብአዊ እርዳታ እያገኙ እንዳልሆነና ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን በመግለጽ፣ መንግሥት የዜጎችን በሰላም የመኖር መብት እንዲያስከብር ተማፅነዋል።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ