«ልመና በቃን፤ ወደ ቀድሞ ቀያችን ተመልሰን ራሳችንን መርዳት እንፈልጋለን» - ተፈናቃዮች | ከይር ታይምስ
አምዶች
የቅርብ ዜና
የቤት ግንባታ ማዳሪጃ ደንብ (ለመንግስት ሰራተኞች) በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኬይር ስታርመር ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ አስታወቁ የቤት ግንባታ ማዳሪጃ ደንብ (ለመንግስት ሰራተኞች) በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኬይር ስታርመር ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ አስታወቁ
ዜና / የሀገር ውስጥ ዜና

«ልመና በቃን፤ ወደ ቀድሞ ቀያችን ተመልሰን ራሳችንን መርዳት እንፈልጋለን» - ተፈናቃዮች

በኢሳያስ ገላው | July 3, 2026

ከኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ጃርቴ ዞን ተፈናቅለው በአማራ ክልል በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች የሰፈሩ ወገኖች፣ ላለፉት ስድስት ዓመታት በከፋ ሁኔታ ውስጥ መቆየታቸውን ገልጸው፤ ወደ ቀድሞ ቀያቸው ተመልሰው ራሳቸውን እንዲረዱ ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጥሪ አቀረቡ።

በደቡብ ወሎ ዞን በጃራ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች ለጋዜጣው እንደገለጹት፤ ለዓመታት በእርዳታ እጅ መጠበቅ ለስነ-ልቦናዊና ማህበራዊ ቀውስ ዳርጓቸዋል። «ጥያቄያችን ግልጽ ነው፤ ወደ ተወለድንበትና ወደ አደግንበት ቦታ መልሱን፤ ሰርተን ራሳችንን እንደግፍ፤ ልመና በቃን» ሲሉ የችግሩን አሳሳቢነት አስረድተዋል። ተፈናቃዮቹ አክለውም፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት የጸጥታና የመሠረተ ልማት ሁኔታዎችን በማመቻቸት ወደ ቀድሞ ይዞታቸው እንዲመልሷቸው በፅኑ ጠይቀዋል።

የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ሥራ አመራር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወይዘሮ ሰርካዲስ አታሌ በበኩላቸው፣ በመጠለያ ጣቢያና ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ ወገኖችን የመመለስ ጉዳይ በትኩረት እየተሠራበት መሆኑን ገልጸዋል። «ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ ከኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አከናውነናል» ብለዋል።

ሆኖም ምክትል ኮሚሽነሯ አያይዘው እንደገለጹት፤ መንግሥት ሁሉንም ተፈናቃዮች የመመለስ ፍላጎት ቢኖረውም፣ የተመላሾችን ደህንነት አስተማማኝ በሆነ መልኩ ማረጋገጥ ቀዳሚውና ወሳኙ ተግባር መሆኑን አመልክተዋል። የጸጥታ ሁኔታው ተፈትሾና ተመላሾች በሰላም መኖር የሚችሉበት ሁኔታ ሲረጋገጥ የመመለስ ሂደቱ እንደሚፋጠን ጠቁመዋል።

በአሁኑ ወቅት ከኦሮሚያና ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በደቡብ ወሎና በሰሜን ወሎ ዞኖች የሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥር ከ64 ሺህ በላይ መሆኑን የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ተፈናቃዮቹ አሁንም በቂ ሰብአዊ እርዳታ እያገኙ እንዳልሆነና ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን በመግለጽ፣ መንግሥት የዜጎችን በሰላም የመኖር መብት እንዲያስከብር ተማፅነዋል።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ በከባድ ወንጀል ተከሰው በቁጥጥር ስር በሚገኙት እነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ የክስ መዝገብ የተካተቱ 23 ተከሳሾች የመከላከያ ምስ...

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ