የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪስት መዳረሻዎችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም ፋና ወጊ ሚና ይጫወታል ተባለ | ከይር ታይምስ
አምዶች
የቅርብ ዜና
የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪስት መዳረሻዎችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም ፋና ወጊ ሚና ይጫወታል ተባለ የቤት ግንባታ ማዳሪጃ ደንብ (ለመንግስት ሰራተኞች) በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪስት መዳረሻዎችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም ፋና ወጊ ሚና ይጫወታል ተባለ የቤት ግንባታ ማዳሪጃ ደንብ (ለመንግስት ሰራተኞች) በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ
ዜና / የሀገር ውስጥ ዜና

የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪስት መዳረሻዎችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም ፋና ወጊ ሚና ይጫወታል ተባለ

በያፌት ግርማ | July 3, 2026

የሀገሪቱን ድብቅ የተፈጥሮና የባህል የቱሪስት መዳረሻዎች ሙሉ አቅም አውጥቶ ለመጠቀምና የዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ የተቀናጀ የመንገድ መሠረተ ልማት ዝርጋታ ወሳኝ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ፈጣን የግንባታ ሂደት ላይ የሚገኘውን የጫኖ - ጨንጫ የመንገድ ፕሮጀክት እና በባህላዊ እሴቱ የሚታወቀውን የዶርዜ ሎጅ የቱሪዝም መዳረሻን በቦታው ተገኝተው በጎበኙበት ወቅት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጉብኝቱ በኋላ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ እንደ ዶርዜ ሎጅ ያሉ ማራኪና ስነ-ምህዳራዊ ውበት ያላቸው የቱሪስት መዳረሻዎች የነበራቸውን እምቅ አቅም በላቀ ደረጃ ጥቅም ላይ ማዋል የሚቻለው ዘላቂና ጥራት ያለው የመንገድ መሠረተ ልማት ሲዘረጋ መሆኑን አብራርተዋል።

የጫኖ - ጨንጫ መንገድ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት እያሳየ ያለው ፈጣን የግንባታ ሂደት ለአካባቢው ሁለንተናዊ ዕድገት አዲስ ተስፋ የሰነቀ መሆኑን ያመለከቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ መሠረተ ልማቱ ተደራሽነትን ከማቃለል ባለፈ የጎብኚዎችን ፍሰት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድገው ገልጸዋል።

"የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋቱ በአካባቢዎቹ ያለውን የቱሪዝም አቅም ሙሉ በሙሉ ለመጠቀም ያግዛል።"ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ይህ ግዙፍ የመሠረተ ልማት አውታር መጠናቀቅ በሀገሪቱ የቱሪስት ፍሰት ላይ ከሚያመጣው አዎንታዊ ተጽዕኖ ባሻገር፣ ለአካባቢው ማኅበረሰብ የላቀ የኢኮኖሚ ትስስርና የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል።

ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ የጀመረችውን የሪፎርም ሥራዎች ተከትሎ፣ የጫኖ - ጨንጫ መንገድ መገንባት የዶርዜን ልዩ ባህላዊ አኗኗር፣ የምግብ አዘገጃጀትና የሸማ ጥበብ ለአገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ቱሪስቶች ይበልጥ ምቹና ተደራሽ በማድረግ ረገድ የጎላ ድርሻ ይኖረዋል ተብሏል።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ በከባድ ወንጀል ተከሰው በቁጥጥር ስር በሚገኙት እነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ የክስ መዝገብ የተካተቱ 23 ተከሳሾች የመከላከያ ምስ...

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ