የብልፅግና ፓርቲ በቁልፍ ክልሎች አሸነፈ፤ ከፊል የምርጫ ውጤቶች ይፋ ሆነዋል |
አምዶች

የዲጂታል ዜናዎች ዕምብርት

የቅርብ ዜና
የብልፅግና ፓርቲ በቁልፍ ክልሎች አሸነፈ፤ ከፊል የምርጫ ውጤቶች ይፋ ሆነዋል የቀይ ባህሩ ቼዝ፣ "የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው" በትሪሊዮኖች የተሰናዳው የ2019 ረቂቅ በጀት ማንን ይታደጋል? የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ረቂቅ በጀት አጽድቆ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተላለፈ ክሪስቲያን ኤሪክሰን በድጋሚ በሜዳ ላይ እራሱን ስቶ ወደቀ፤ ጨዋታው ተቋርጧል የቀይ ባህር አዲስ ሰንሰለት፦ የፕሬዝዳንት ኢሳያስ ድንገተኛ የካይሮ ጉብኝት እና የአፍሪካ ቀንድ እጣ ፈንታ የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የግብፅ ጉብኝት እና የቀጠናው የፖለቲካ ትኩሳት የዲሞክራሲ ማሽን ፈታኝ ሰዓታት፦ የምርጫ ውጤት ማዳመር ለምን ዘገየ? የሚሊዮኖች ህልም እና የሚሊዮኖች ዋጋ፡ የአዲሶቹ ኮንዶሚኒየሞች ይፋዊ የዲዛይን እና የክፍያ ዝርዝር መግለጫ ታሪክ ራሱን ይደግማል? ከኢሕአዴግ ውድቀት እስከ 7ኛው ብሔራዊ ምርጫ ማግስት የብልፅግና ፓርቲ በቁልፍ ክልሎች አሸነፈ፤ ከፊል የምርጫ ውጤቶች ይፋ ሆነዋል የቀይ ባህሩ ቼዝ፣ "የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው" በትሪሊዮኖች የተሰናዳው የ2019 ረቂቅ በጀት ማንን ይታደጋል? የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ረቂቅ በጀት አጽድቆ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተላለፈ ክሪስቲያን ኤሪክሰን በድጋሚ በሜዳ ላይ እራሱን ስቶ ወደቀ፤ ጨዋታው ተቋርጧል የቀይ ባህር አዲስ ሰንሰለት፦ የፕሬዝዳንት ኢሳያስ ድንገተኛ የካይሮ ጉብኝት እና የአፍሪካ ቀንድ እጣ ፈንታ የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የግብፅ ጉብኝት እና የቀጠናው የፖለቲካ ትኩሳት የዲሞክራሲ ማሽን ፈታኝ ሰዓታት፦ የምርጫ ውጤት ማዳመር ለምን ዘገየ? የሚሊዮኖች ህልም እና የሚሊዮኖች ዋጋ፡ የአዲሶቹ ኮንዶሚኒየሞች ይፋዊ የዲዛይን እና የክፍያ ዝርዝር መግለጫ ታሪክ ራሱን ይደግማል? ከኢሕአዴግ ውድቀት እስከ 7ኛው ብሔራዊ ምርጫ ማግስት
ፖለቲካ / ምርጫ

የብልፅግና ፓርቲ በቁልፍ ክልሎች አሸነፈ፤ ከፊል የምርጫ ውጤቶች ይፋ ሆነዋል

በያፌት ግርማ | June 11, 2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ22 የምርጫ ክልሎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለክልል ምክር ቤት የቀረቡ ዕጩዎችን ውጤት ይፋ ማድረጉን አስታወቀ። ቦርዱ ውጤቱን ይፋ ያደረገው ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ በስካይ ላይት ሆቴል በሚገኘው ጊዜያዊ ጣቢያው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።

በዚሁ መግለጫ መሠረት ቦርዱ ከአማራ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአንድ፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሦስት፣ ከኦሮሚያ ክልል ለክልል ምክር ቤት ዘጠኝ እና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰባት፣ እንዲሁም ከሶማሌ ክልል ለክልል ምክር ቤት በሁለት የምርጫ ክልሎች ላይ የቀረቡ ዕጩዎችን ውጤት በይፋ አሳውቋል።

የምርጫ ውጤቱን ዝርዝር በተመለከተ፤ በአማራ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለመወዳደር በጎንጎን ምርጫ ክልል የብልፅግና ፓርቲ በብቸኛነት ዕጩውን ያቀረበ ሲሆን፣ ከፍተኛውን ድምፅ ማግኘቱ ተገልጿል። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሦስት ምርጫ ክልሎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል በሁሉም ምርጫ ክልሎች የብልፅግና ፓርቲ ዕጩዎች ከፍተኛውን ውጤት ማግኘታቸው ተመልክቷል።

በተመሳሳይ ሁኔታ ቦርዱ በኦሮሚያ ክልል ለክልል ምክር ቤት በዘጠኝ እና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰባት የምርጫ ክልሎች መካከል ባካሄደው ውድድር፤ በሁሉም የክልል እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች የብልፅግና ፓርቲ ዕጩዎች ከፍተኛ ውጤት ማግኘታቸውን በመግለጫው አስታውቋል።

በሌላ በኩል በሶማሌ ክልል ለክልል ምክር ቤት ዕጩ በቀረበባቸው ሁለት የምርጫ ክልሎች፤ በሁለቱም አንደኛውን ከፍተኛ ውጤት የብልፅግና ፓርቲ ዕጩ ያገኘ ሲሆን፣ በሁለተኛው የምርጫ ክልል ደግሞ የኦጋዴን ነፃነት ግንባር (ኦነግ) በዕጩነት ያቀረባቸው ተወዳዳሪ አራተኛውን ከፍተኛ ውጤት ማግኘታቸውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መግለጫ ያሳያል።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ