ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ዜጎቿ ደኅንነት እንዲጠበቅ ጠየቀች | ከይር ታይምስ
አምዶች
የቅርብ ዜና
በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኬይር ስታርመር ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ አስታወቁ በ7ኛው አጠቃላይ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ ድምፅ በማግኘት ማሸነፉ ተገለጠ በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኬይር ስታርመር ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ አስታወቁ በ7ኛው አጠቃላይ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ ድምፅ በማግኘት ማሸነፉ ተገለጠ
ፖለቲካ / ዲፕሎማሲ

ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ዜጎቿ ደኅንነት እንዲጠበቅ ጠየቀች

በያፌት ግርማ | July 1, 2026

የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደዔታ አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ፣ በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ደኅንነት ዙሪያ በአዲስ አበባ ከደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኖንኬባ ሎሲ ጋር ትናንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያዩ። ይህ ውይይት የተካሄደው በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ የተለያዩ አካባቢዎች በውጭ ዜጎች፣ በተለይም በኢትዮጵያዊያን ፍልሠተኞች እና ነጋዴዎች ላይ እየተፈጸሙ ያሉ ጥቃቶች ማገርሸታቸውን ተከትሎ ነው።

ሚንስትር ደዔታ ብርሃኑ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፣ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚፈጸሙ ተደጋጋሚ ጥቃቶች እና የማንገላታት ድርጊቶች የኢትዮጵያን መንግሥት በእጅጉ አሳስበውታል። የዜጎች ደኅንነት መከበር ለኢትዮጵያ መንግሥት ቀዳሚ ተግባር መሆኑን የጠቆሙት አቶ ብርሃኑ፣ መሰል ጥቃቶች በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ታሪካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳያሻክሩ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

"በቅርቡ በውጭ ዜጎች እና በወገኖቻችን ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶች እጅግ አሳሳቢ ናቸው" ያሉት ሚንስትር ደዔታው፣ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት የኢትዮጵያዊያንን ደኅንነት ለመጠበቅ እና መሰል ጥቃቶች ዳግም እንዳይከሰቱ ጠንካራ እና ተግባራዊ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል። በተለይም በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ንብረት እንዳይዘረፍ እና ህይወታቸው አደጋ ላይ እንዳይወድቅ የጸጥታ አካላት ጥበቃ እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።

አምባሳደር ኖንኬባ ሎሲ በበኩላቸው፣ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ማንኛውንም ዓይነት የጥላቻ ጥቃት እና የሕግ ጥሰት በጽኑ እንደሚያወግዝ ገልጸዋል። መንግሥታቸው ጥቃቱን "ከደቡብ አፍሪካ እሴቶች ጋር የሚቃረን" ሲል መግለጹን ያስታወሱት አምባሳደሯ፣ በአሁኑ ወቅት ጥቃቱን በፈጸሙ አካላት ላይ ሰፊ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል።

አምባሳደሯ አክለውም፣ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንና የምርመራው ውጤት እንደተጠናቀቀ በይፋ ለኢትዮጵያ መንግሥት እንደሚያጋሩ ቃል ገብተዋል። በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ ሁለቱም ወገኖች የዜጎችን መብት ለማስከበር እና ቀጣናዊ ሰላምን ለማስጠበቅ በዲፕሎማሲያዊ እና በጸጥታ ዘርፎች በቅርበት ለመስራት ተስማምተዋል።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ በከባድ ወንጀል ተከሰው በቁጥጥር ስር በሚገኙት እነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ የክስ መዝገብ የተካተቱ 23 ተከሳሾች የመከላከያ ምስ...

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ